Get Mystery Box with random crypto!

Abu_Oubeida~channel

لوگوی کانال تلگرام abuoubeida — Abu_Oubeida~channel A
لوگوی کانال تلگرام abuoubeida — Abu_Oubeida~channel
آدرس کانال: @abuoubeida
دسته بندی ها: حیوانات , اتومبیل
زبان: فارسی
مشترکین: 5.05K
توضیحات از کانال

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم
{ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


آخرین پیام ها 12

2022-02-28 14:23:39 አቶ ንጽህና ጥበቃ
――――――

አንዳንድ ሰዎች ምግብ ሲበሉ ወሃን መጠጣት በፈለጉ ጊዜ የውሃ ብርጭቆው በምግብ እንዳይለወስ (እንዳይቆሽሽ) በመስጋት በግራ እንጃቸው ይዘው ይጠጣሉ።በቀኝ እጄ ብጠጣ የውሃ ብርጨወቆው ከምግብ ጋር እንዳይለወስ ሰግቼ ነው ይላል።ይለወስ(ይቆሽሽ)።ቢቆሽሽ ምግብ አይደደል የነካው?በሽንትና በሰገራ ነው የተለወሰው? በምግብ ተለወሰ(ቆሸሸ) ይታጠባል።

የውሃ ብርጭቆውን ከስር(በመቀመጫው) በኩል መዳፍህ ላይ በአውራ ጣትህና በአመልካች ጣትህ በቀለበት መልኩ አድርገህ አጣብቀህ መያዝ ትችላለህ።ምግብ ቢነካውን እንኳን ውስን ነው ብዙ አይነካውም።ብርጭቆውን ምግብ እንዳይነካው ብለህ በግራ እጂህ የምትጠጣ ከሆነ ምክንያት የለህም።በግራ እጅህ አንዳትተጣ የተነገረህ ሀራም በሆነ መልኩ ነው።ብርጭቆውን ምግብ እንዳይነካው በመስጋት በግራ እንጅ ለመጠጣት ይሄ ምክንያት አይሆንም።ሀራም ነው።በግራ እጂህ እንደትጠጣ የሚፈቀድልህ ቀኝ እጂህ ምግብም ሆነ የውሃ ብርጭቆ መያዝ የማይችል(ሽባ)፣ የተሰብረ ወይንም ቁስለት ያለው ሁኖ (ምግብ)ወደ አፍህ ማድረስ የማይችል ሲሆን ነው።

ከሙሐመድ ቢን ሷሉህ አል_ኡሰይሚን የሪያዱ አስሷሊሂን ሸርሕ ላይ ተነካክቶ የተወሰደ።(2/810)

አቡ_ዑበይዳ
https://t.me/AbuOubeida
949 views11:23
باز کردن / نظر دهید
2022-02-28 13:40:39 የደጋፊ መጥፎ

በአሏህ ስም ልጀምር ቀጥሎም ምስጋና
ሶለዋቱም ይውረድ በሰው ልጅ ናሙና
በሙሐመድ አሚን ባሉት ከመድና
ሰላም ይስፈን እስኪ በተከታይ ፋና
የሳቸውን ፈለግ በጠበቁት ጀግና
ላይ በሶሓቦቹ እንቁ ባለዝና
አልሐምዱሊላህ ለዚህ አበቃና
ለማይቀር ውሳኔው ለድንቅ የሱው ሱና
ያልጠበቅነዉ ክስተት አሞናል በጠና
እስኪ አሏህ ያሽረን አሚን እንበልና
በሶብር እንታገዝ ስግደት ጨምሩና
አሏህ ለሐቅ ይምራን አንገት ይበል ቀና
አያስደስትብን ጠላት በዝቷልና
በሐቅ ይሰብስበን ባጢሉ ይጥፋና
አንድ እኮ ነች ሐቋ ልዩነት ለምና?
እስኪ ቅድሚያ ይግባን ይህ ታላቅ ፈተና
ከአሏህ መሆኑን የሱው ድንቅ ሱና
እውነተኛ ባሮች ከአስመሳይ ገናና
ለመለየት ሲሻ አሏሁ ረቡና
ረጋ በማለት በዱዓ እንበርታና
ለነፍሳችን አዛኝ ጥንቁቅ እንሁንና
አቧራው እስኪቦል ከለል እናርግና
ጉዳት እንጠንቀቅ ጥቅሙ ይዘግይና።
በሰው ልጅ መካከል ልዩነት አለና
አደራ ወንድሞች እህቶች ስሙና
በፍትሕ ላይ ቁሙ ተቅዪ ሁኑና።
የምን መደናገር የምን መቸኮሉ
ቅድሚያ ምን ላይ ቆመን አሁን ጠፋን ውሉ
እንዴ...!
ምነው እህት አለም ምን ሆንክ ወንድሜ
ለዚች ድፍርስ ዱኒያ ለአጭሯም እድሜ
የምን መልፈስፈስ ነው የምን ጭንቅ ያላቅሜ
በቃ አሁንስ በቃ ለምን መቆዘሜ
ሆነ በአሏህ ሁንታ አልሐምዱሊላሂ እስከዘላለሜ
የዚህ ትውልድ አባል አድርጎኝ ልይ ቆሜ
ሐቅ ነግሳ ስትወጣ እኔም ተሸልሜ
በሐቅ ተውቤ ልኑር ተደምሜ
በአሏህ እገዛ ስህተቴን አርሜ
በሰለፎች ፋና እንደዔሊ አዝግሜ
በዛው ብቻ ልጓዝ ባልሮጥም ቀድሜ
በሐቋ ላይ ልሙት በኢኽላስ ከርሜ
ሙታበዓን ይዤ ኸይራትን ቃርሜ።
በል በይ በሉ ብዬ ለዛሬው መነሻ
መግቢያ ያደረኩት መልእክቴን ማድረሻ
ገጠር ሆኜ ርቆኝ ካሉበት መድረሻ
በአካል ለሹራ እርቅ መቀስቀሻ
ብትሆን ብዬ ነው ግጥሜ ማስታወሻ።
የሚያደናቅፍ እርቅ አደጋው የከፋ
ትልቁ ፈተና ፀብን እያስፋፋ
ስራ የሚያስፈታን በማስቆረጥ ተስፋ
የሸይጧን ጉትጎታ ሐቅን የሚያጠፋ
መሆኑን እንወቅ ብዙም ሳንለፋ
ሐድሱም ይታወስ ይሰራበት ይፋ
ይህ ነው ችግራችን በጣም የተስፋፋ
አንድ ሰው ሲበድል የሚያግዝ ሲጠፋ።
እንደት እንገዘው ሲበድል ካላችሁ
እጁን በመያዝ ነው ምላሱን ዘግታችሁ
ዝም አስብሉትና ትቂት አስታግሳችሁ
ምከሩት ይረዳ ስሜት አርቃችሁ
አሳዩት ስህተቱን ፍንትው አድርጋችሁ
ደጋግሙለት በጣም ዱዓ እያረጋችሁ
ከገባው እሰየው አሏህ ወፍቋችሁ
እንቢ ካለስ ከዛ ትተውታላችሁ
የነቀፈው ሁሉ አይሁን ጠላታችሁ
ሸይጧናዊ መንሐጅ ፍፁም እርቃችሁ
"ከጠፋ እኔም ልጥፋ" ማለቱን ትታችሁ
የአበልቃሲም ፈለግ ሆኖ ዋስትናችሁ
ከዚህ ተቃራኒ መሆኑን አውቃችሁ
ሐቁን ተከተሉ ግለሰብ ትታችሁ
ማንን ሽቶበት ነው ለሚል ጥያቄያችሁ
ከኔ አትጠብቁ መልስ እያወቃችሁ
ኪታቡሏህ ሱናን በማጥበቅ ይዛችሁ
ከዚያም በመቀጠል ዑለማ አሉላችሁ
ታማኝ መካሪዎች አዳምጡ አትኩራችሁ
ህሌና እየዳኜ በራስ ላይ ፈርዳችሁ
ለሐቅ ዱዓ አርጉ ባጢል እርቃችሁ
አትፈላፈሉ ቅርብ ነው ጊዜያችሁ
ሐቅ ይፋ ይወጣል ጠብቁ ታግሳችሁ
በመልካም ስራ ላይ ቀጥሉ ፀንታችሁ
ትላንት ባጢል ብሎ ዛሬ ከካዳችሁ
ደግሞም ይባስ ብሎ ሐቅ ሆነ ካላችሁ
በጭፍን መከተል ይቅር ተጋግዛችሁ
ዐቅሉን አስመርምሩ "ሸርጡ"ን አትኩራችሁ
እንኳን በዳዕዋ ፈን ለአርካነ-እስላማችሁ
ለሶላት "ዐቅል" ነው ወሳኙ ሐብታችሁ፤
ባጢል ተወጋጅ ነው ብሏል አምላካችሁ
ሐቅንም ከባጢል ባጢል ከሐቃችሁ
አያቀላቅልም አዛኙ ጌታችሁ
ብቻ ተማፀኑት "ኒያ" አሳምራችሁ፤
አትደናገሩ ሌላ አደናግራችሁ
የሰለፎች ፋና ፍንትው ብሎላችሁ
ለትኩረት እይታ ያብራ ብሌናችሁ
ከደሊል ጋር ዙሩ ከሱናው አብራችሁ
ለምንስ ግለሰብ ተተቸ ብላችሁ
በከንቱ ሙገሳ ራስ ሸውዳችሁ
ስህተት አትሸፍኑ በግልፅ ካያችሁ
መጥፎን ተቃወሙ እንደየድርሻችሁ
እኔ ገጠር ሆኜ በጣም ርቄያችሁ
አልደናገርም ከተማ ያላችሁ
ግለሰብ ተከታይ ሳልሆን ወንድማችሁ
የአሏህ ባሪያ ሁኑ አሕመድ አርዓያችሁ
እሱን እንከተል ለሞዴል በቂያችሁ
ሩሱሉሏሂ መሆኑን አውቃችሁ
"ሹቡሐ" ባህር ውስጥ ሸይጧን አይጣላችሁ
በስሜት ማእበል እያሰመጣችሁ
ይታረም ተሳሳች ሰው ነውና አውቃችሁ
ንገሩት በይፋ ኢኽላስ ላይ ሆናችሁ
በጥፋቱ መጠን ክብሩን ጠብቃችሁ
መልካሙን አትካዱ ተመቸን ብላችሁ
ትንሽ ክፍተት ካለም ንፋሱን ዘግታችሁ
በሸይጧን ላይ እርዱት ይህን ወንድማችሁ
ፍልሚያ ላይ ይሆናል ምን አሳወቃችሁ
ያሸንፍ ድል ያድርግ አብሽሩት ሁላችሁ
በጥፋቱ ሳይሆን በሐቁ አርማችሁ
ባቅማችሁ ሞክሩ ከተቀበላችሁ
እሱም ስራ ላይ ነው ለፍቷል ለድናችሁ
ምናልባትም አሏህ ሰበብ ቢያደርጋችሁ
በፍትሕ ላይ ቁሙ ይህን ካልቻላችሁ
ከኔ እሱ ይሻላል በማለት መርጣችሁ
ለአስታራቂ አግዙ አደራ ያልኳችሁ
ቤንዚን ሲያርከፈክፍ ሸይጧን ጠላታችሁ
ክብሪት አትጫሩ ፊትናን ተጠምታችሁ
ቢያንስ ሌላ ባትችሉ ዝም አያቅታችሁ
ምነው ይታረቁ ... ሰው አያስጠላችሁ
የሱና ሰው አንሷል ንቁ እስኪ እባካችሁ
ሰው ማራቅ አንምረጥ በሐቅ አስታርቃችሁ
ማቅረብ መቃረቡን አስቡ ስላችሁ
ነፍስያን ያሸንፍ ማን ይሁን ምናችሁ
መስፈርቱ ሐቅ ይሁን ለኪ ሚዛናችሁ
የደጋፊ መጥፎ አትሁኑ እባካችሁ።

አቡ ሐኒፋ ዐብዱልከሪም (ከገጠር)
ቅዳሜ፣ የካቲት 19፣ 2014 ዓ.ል.
512 views10:40
باز کردن / نظر دهید
2022-02-28 11:14:28 ወደ ተብዲዕ እና ወደ ተክፊር መቸኮል አያስፈልግም
https://t.me/FewaidSheikhMuhammedZain/193
748 views08:14
باز کردن / نظر دهید
2022-02-27 20:29:31 የውይይት ጥሪ
~~
1- ለሸይኽ ዐብዱልሐሚድ፣
2- ለሸይኽ ሐሰን ገላው
3- ለኡስታዝ በሕሩ ተካ
4- ለኡስታዝ ዩሱፍ አሕመድ
5- ለወንድም ሑሴን ሙሐመድ አሲልጢ
6- ለወንድም ዐሊ ሑሴን
-----
ከሆነ ጊዜ ጀምሮ የሚራገበው ፊትና ከዛሬ ነገ ከመሻሻል ይልቅ እየባሰበት መሄዱ ለማንም የሚታይ ነው። ጉዳዩ ይበልጥ በተራገበ ቁጥር ብዙ ሰው እየተፈተነ እንደሆነ እያየን ነው። ፊትናው ምንም እንኳ ለጊዜው ብዙ ሰው እየጎዳ ቢሆንም ከማንም በላይ የሚጎዳን ግን እኛኑ እራሳችንን ነው። ምክንያቱም በያንዳንዱ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በኛ ሰበብ ከመስመር በሚርቀው፣ ግራ በሚጋባው፣ በደል ላይ በሚሰማራው ሁሉ ከአላህ ፊት ተጠያቂ እንሆናለንና።
ስለዚህ እባካችሁን! በአቋማችሁ እርግጠኝነት ካላችሁ በሰከነ መልኩ ህዝብ እየታዘበን እንወያይ። እንተራረም። ስህተቱ ከኛ ከሆነ በአላህ ስም እምላለሁ ለመመለስ ዝግጁ ነኝ። ሌሎችም ወንድሞች እንዲሁ። እናንተም በዚህ መልኩ እራሳችሁን አዘጋጅታችሁ ቅረቡ።

1- ፈቃደኝነታችሁ ከታወቀ ውይይቱ ጤናማ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የሚያግዙ ነጥቦችን አብረን እናወጣለን።
2- መካተት አለበት የምትሉት ሰው ካለም ይካተታል።

ለምን ባደባባይ ጥሪ ማድረግ አስፈለገ የሚል ሊኖር ይችላል። ምክንያቱ ሁለት ነው፡፡
1ኛ፦ ጉዳዩ ምስጢር ሳይሆን ይልቁንም በሰፊው የሚራገብ ስለሆነ፣
2ኛ፦ ከዚህ በፊት ለብቻ የተደረገው ውይይት ፍሬ አልባ ከመሆኑም በላይ ጭራሽ ነገሮች ይዘታቸው እየተቀየረ ሲናፈሱ ስለነበር ነው።
~
ስለዚህ በግልፅ ተወያይተን ቢቻል እንተራረም። ካልሆነም ሑጃ ለማቆም ይረዳችኋል።
(لیَهۡلِكَ مَنۡ هَلَكَ عَنۢ بَیِّنَةࣲ وَیَحۡیَىٰ مَنۡ حَیَّ عَنۢ بَیِّنَةࣲۗ)
ከኛም ይሁን ከናንተ በተነሳ ሀሰተኛ ዘመቻ፣ አሉባልታ፣ የተሳሳተ ትንታኔ ምክንያት የተሸወደ ካለም ውይይታችንን ተከታትሎ የሚበጀውን ይወስን።
እንደምታውቁት ሶሐባው ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ ከኸዋሪጅ ጋር ተወያይተዋል። ከሌሎችም ሰለፎች እንዲሁ ተመሳሳይ ነገር ተገኝቷል። ይህን የምጠቅሰው ለውይይት ተጠርተው "ከሙብተዲዕ ጋር መወያየት አይቻልም" በሚል ማመሀኛ የሸሹ ሰዎች ሁኔታ እንዳይደገም ነው።
ስለዚህ ቢሆንልን እንግባባለን። ካልሆነም የደረስንባቸውን ነጥቦች ሁለታችንም ለምናምንባቸው ዐሊሞች በጋራ ፅፈን እናቀርባለን።

* ይህንን ጥሪ ያነበባችሁ በተለይም ደጋግማችሁ "ብትወያዩ" ስትሉ የነበራችሁ በአድራሻቸው በመደወል ወይም በመላክ ወይም በአካል ቀርቦ በማናገር መልእክታችንን አድርሱልን።
* ለውይይቱ ፈቃደኛ ከሆናችሁ ከስር በቀረበው ሊንክ ግሩፑን እንድትቀላቀሉ እጋብዛለሁ። ሌሎቻችሁ በዚህ ፊትና የተነካኩ ወይም ግራ የተጋቡ፣ ወይም መከታተል የሚፈልጉ ሰዎችን ብቻ አስገቡ። ያገኛችሁትን ሁሉ ዝምብላችሁ add አታድርጉ።
-
https://t.me/+AkvdZdEAY-FiZjM0
241 views17:29
باز کردن / نظر دهید
2022-02-15 21:46:17 እራሴ ከድርጊቱ ሳልቆጠብ ሌሎችን አልከለክልም!!
――――――

አንድ ሰው ሌሎችን በመልካም ሲያዝ አስቀድሞ በሚያዘው ነገር ላይ እሱ መልካምን ሰሪ ሊሆን፤ከሚከለክለው መጥፎ እሱ አስቀድሞ ከዛ ድርጊት የተከለከለ ሊሆን መስፈርት ነው? ወይስ አይደለም? የኡለሞች መናጋት አለ።ትክክለኛው ግን መስፈርት አይደለም የሚለው ነው።ምንም እንኳን በሚያዘው ባይሰራና ከሚከለክለው ከሆነው መጥፎ ለራሱ ባይከለከል እንኳን ሰዎችን በመልካም ያዛል።ከመጥፎ ይከልክላል።እኔ እራሴ የማዝበትን መች ሰራሁበት?፤ከምከለክለው መች ተከለከልኩ?ብሎ በመልካም ማዘዝና ከመጥፈፎ መከልክል የተወ እንደሆነ፡በወንጀሉ ላይ ሌላ ወንጀልን ጨምሯል።ምንም እንኳን ለራሱ መልካምን የማይሰራ ከመጥፎ የማይከለክል ቢሆንም፡ በመልካም ሊያዝ ከመጥፎ ሊከለክል ግዴታው ነው።ነገር ግን ብዙ ጊዜ በተፈጥሮ የሰው ልጅ ወደ ማይሰራው ስራ ሰዎችን አይጠራም ከማይከለከለው መጥፎም ሰዎችን አይከለክልም።ያፍራል።ይፈራል።ግዴታው ግን ምንም እንኳን እሱ ባይሰራውም ሸሪዓው በደነገገው ሊያዝና ከከለከለው ሊከለክል ነው።ምክንያቱም ይህ እያንዳንዱ አንዱ ከሌላኛው የተጠለ ግዴታ ነው¹።ሙሐመድ ቢን ሷሊል አል_ኡሰይሚን ሸርሕ ሪያዱሷሊሒን(1/569)
――――
(¹)ለራስ በመልካም መስራትና ከመጥፎ መከልከል እራሱን የቻል አንድ ግዴታ ነው።ሌሎችን በመልካም ማዘዝ እና ከመጥሆ መከልክል ሌላኛው ራሱን የቻለ ግዴታ ነው።

አቡ_ዑበይዳ
https://t.me/AbuOubeida
355 views18:46
باز کردن / نظر دهید
2022-02-14 13:37:49


‏قال العلامة عبد العزيز بن باز - رحمه الله -:

ولا يجوز التساهل مع البنات الصغار في لبسهن
للملابس القصيرة، لأنّ تربيتهن عليه يفضي إلى
اعتيادهن له، وكراهيتهن لما سواه إذا كبرت.

التبرج وخطره - (ص: ١٦)
397 views10:37
باز کردن / نظر دهید
2022-02-14 08:30:18 አጭር ምክር

በኢብኑ ሙነወር ላይ ሲነሱ ለነበሩ ውዥንብሮች በበቂ መልስ ተዳሷል

ኢብኑ ሙነወር ከቢድአ ባለቤቶች ጋር መተባበር ይቻላል ብሏል?
እውን ኢብኑ ሙነወር የቢድአ ሰው ማወደስ ይቻላል ብሏልን?

ከራሱ አንደበት እውነታው ተረዱ

https://t.me/IbnuMunewor
515 views05:30
باز کردن / نظر دهید
2022-02-13 15:06:18 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته،
ማሳሰቢያ፦ ከዚህ በፊት እንደሚታወቀው በሸይኽ አወል ቢን አሕመድ አል_ኬሚሴ እየተሰጠ ያለው የተፍሲር ትምህር በቀጥታ ስርጭታ በዚሁ(በ አቡ_ዑበይዳ) ቻነል ሳካፍላችሁ ቆይቻለሁ።ይሁንና ከዛሬ ጀምሮ የሚሰጠውን የሸይኹን የተፍሲር ትምህርት በራሳቸው ቻነል ላስተላልፍላችሁ ወስኒያለሁ።ስለሆነም ከስር ባለው በሸይሁ "ገፅ"ጆይን በማለት ትምህርቱን ከዚህ በፊት ትከታተሉ እንደነበረው መማር የምትችሉ መሆኑ ላስገነዝብ እወዳለሁ።
https://t.me/SheihkAbuAmarAwolIbnuAhmed
በቀጥታ ስርጭት ትምህርቱ ላይ የኔትወርክ እና መሰል መቆራረጥ ካለ ቀጥታ እዚሁ የኔ ገፅ ላይ መጥታችሁ ኮመንት ማስቀመጥ ትችላላችሁ።
https://t.me/AbuOubeida
778 viewsedited  12:06
باز کردن / نظر دهید
2022-02-11 21:49:23 تفسير القرآن:

لشيخنا أبي عمار أول بن أحمد الخميسي
سورة العمران(١١_٢٧)

موضع الدراسة مركز بن عباس الإسلامي
(في مدينة الخميسي)

للاضمام بالقناة
https://t.me/SheihkAbuAmarAwolIbnuAhmed
966 views18:49
باز کردن / نظر دهید
2022-02-11 15:33:36 ( وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ )
الروم (21)

ቻው ቻው ላጤነት መንገዱን ጨርቅ ያድርግህ። የስንት አመት ባለረደረበዬ እንደዚህ ትቼህ ባንድ ጊዜ ተለየሁህ አይደል? !ቻው ስለይህ በእንባ¡¡


በቃ! ከዚህ ቡኃላ እኔን "ላጤ"እያሉ መሳደብ አይቻልም።

የወንድማችሁ "አቡ_ዑበይዳ" & የእህታችሁ "ኡሙ ፈዛን"የኒካህ ፕሮግራም ትላንት ተፈፅሟል።
955 views12:33
باز کردن / نظر دهید